Skip to main content
እስልምናን ለማጥቃት ሲል ግን በእስልምና የተማረከው ጀግና..! ክፍል 1 ዛሬ እስኪ አንድ ጀግና ላስተዋዉቃችሁ እስልምናን ለማጥቃት ሲል ግን በኢስላም የተማረከ ጀግና share አድርጉት በልጅነት እናትና አባቱ ከአገር ይወጣሉ። በዚህ አጋጣሚ በእናቱ እናትና አባት በአያቶቹ እጅ ያድጋል። ክርስትናም አዲሱ ገበያ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ያስጠምቁታል። በልደታ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በር ላይ አንድ ፕሮቴስታንት ኢየሱስ ጌታ ነው እያለ ሲሰብክ ቴሌ የቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ገፍትረው በድንጋይ የማርያም ጠላት እየተባለ በድንጋይ ወግረው ሲገሉት ያያል። በመቀጠል ጎፋ ገብርኤል ደጅ ላይ ድግምት የተሰራበት ሰው እንቁራሪት ሲያስታውክ ያያል። ያንን ድርጊት ሲያይ በቀጥታ ከኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ይሰናበታል። በመቀጠል ኢየሱስ ጌታ ነው ወደሚሉት ፕሮቴስታንት ሰሜን መሰረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በመነጋገር ኢየሱስን የግል አዳኙ አድርጎ ተቀበለ። የደህንነት ትምህርት ከተማረ በስድስት ወሩ የውኃ ጥምቀት ወስዶ ተከታታይ ኮርስ ወሰደ። በዚህ ወቅት ላይ መጽሐፍ ቅዱስን ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ በግሉ ማንበብ እና የተለያዩ ማብራሪያዎችን መመልከት ጀመረ። ይህንን የአብነት ትምህርት እየተማረ በተጓዳኝ የአስኳላ ትምህርት ኢለመንተርይ ጨርሶ ሃይስኩል ገባ። ከዚያ ከሃይስኩል ወደ ፕሪፓቶቴርይ ከፕሪፓራቶሪ ወደ አምስት ኪሎ ዩንቨርስቲ ቅርንጫፍ ወደሆነ የህንጻ ምህንድስና 5 ዓመት ካጠናቀቀ በኃላ። ከአገር ይወጣል። ካገር ከወጣ በኃላ ስቶክሆል ዩንቨርስቲ በማቴሪያል ኢንጅነሪንግ እየተማረ እያለ በግቢ ውስጥ በሚደረገው የፍልስፍና የስነ ልቦና እና የስነ አመክንዮ ውይይት ላይ መሳተፍ ጀመረ። አንድ ጓደኛው ፓል ቶክ የሚባል የውይይት መድረክ አለ እዛ ገብተህ ብታተረማምሳቸው ጥሩ ነበር አለው። ወደ ሳይበሩ ዓለም ሲመጣ አጋጣሚ ክርስትና እና እስልምና የሚፋጠጡበት መድረክ ነበር። ከኢትዮጵያ ኡስታዝ አቡሃይደር ከፈረንሳይ በረከት የሚባሉ ጠንካራ ተወያዮች ሁለት የተለያየ ግሩፕ መስርተው ይወያዩ ነበር። በዚህ ወቅት ነው የክርስትናውን መድረክ የተቀላቀለው። ይቀጥላል...... እርሶ ሰለምቴ ኖት..!? እንግዲያውስ ታሪኮ ለሌሎች መማሪያ ይሆን ዘንድ ። ለአንዲት ነፍስ የሒዲያ ሰበብ ሊሆን ይችላልና ታሪኮን ያካፍሉን ። አድራሻችን ፦ http://t.me/Selmeta ቴሌግራም 00966597257492 http://t.me/Ohanw9 00966503917209 http://t.me/OBintMahmud በዋትስ-አፕ 00966554225870 https://t.me/Quran_is_life_Sari_A የፕሮግራሙ መገኛ ዩቱብ https://youtu.be/aU23u6NuZTo የአስሓቡል የሚን ማህደር፦ https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg ሠለምቴ የሆኑ ይምጡ ለመሥለም የሒዳያ ሠበበዎን ያካፋሉን! እኛም ለሌሎች አሥተማሪ በሆነ መልኩ እያዘጋጀን እናቀርባለን።
Popular posts from this blog
Comments
Post a Comment