በአንድ ወቅት ነቢዩሏህ ሱለይማን ዐለይሂ ሰላም አንዲት ጉንዳን ከድንጋይ መኃል ያገኛሉ ። ጉንዳኗም አብሯት አንድ ፍሬ ስንዴ አጠገቧ ነበር ። ነቢ ሱለይማንም ዐለይሂ ሰላም " እዚህ ድንጋይ መኃል እየኖርሽም አሏህ ይረዝቅሻልን ?! " ብለው ይጠይቋታል ። እርሷም " አዎን አሏህ ምን ይሳነዋል ?! " ብላ መለሰች ። " ለመሆኑ ይህች አንዷ የስንዴ ፍሬ ለምን ያክል ጊዜ ትበቃሻለች " ሲሉም ይጠይቋታል ። እርሷም " ለአንድ ዓመት ይበቃኛል !! " ስትል መለሰች ነቢዩ ሱለይማንም ዐለይሂ ሰላም " እስቲ እኔ ዘንድ ለአንድ አመት ላቆይሽ " ብለው በመውሰድ አንድ የስንዴ ፍሬ ሰጥተው ያስቀምጧታል ። በአመቱም ጉንዳኗን ለማየት ወዳለችበት ሲሄዱ ግማሹን የስንዴ ፍሬ በልታ ግማሹን አስቀምጣዋለች ። ነቢዩ ሱለይማንም ተደንቀው " ለአንድ ዓመት አንድ የስንዴ ፍሬ ይበቃኛል ብለሽኝ አልነበረምን ?! ታዲያ ግማሹን በልተሽ ግማሹን ለምን ተውሽው ?! " ሲሉ በአግራሞት ይጠይቋታል ። እርሷም " መጀመሪያ ለአንድ አመት አንድ ፍሬ ስንዴ ይበቃኛል ያልኩት እኮ በአሏህ እጅ ላይ ሆኜ ነው !! አሁን ግን በአንንተ እጅ ስለገባሁ ሰው ነክና ልትረሳኝ ትችላለክ ብዬ ግማሹን በልቼ ግማሹን ደግሞ ለምናልባት ብዬ አስቀረሁት !! " ስትል መለሰችለት ። ከጉንዷን ብልህነትን እንማር ። ተስፋችን በአሏህ ላይ ይሁን ።

Comments

Popular posts from this blog

ከወንድም አቡበከር ትረካ የተወሰደ አቢ ደምደም ማን ነው ? እንደ አቢ ደምደም መሆን የሚችል ማን ነዉ?? _________ አቢ ደምደም ደግሞ ማነው የብዙዎቻችሁ ጥያቄ እንደሚሆን እገምታለሁ ተከተሉኝማ ልንገራችሁ። አቡ ዳዉድና ጦብራኒ ከአነስ ኢብኑ ማሊክ ረድያላሁ አንሁ እንደዘገቡት የአላህ መልዕክተኛ ሰለላህ አለይሂ ወሰለም አንድ ቀን ለሰሀቦቻቸዉ ከእናንተ መካከል እንደ አቢ ደምደም መሆን የሚችል ማነው ?? በማለት ጠየቋቸው ሰሀቦችም የአላህ መልዕክተኛ ሆይ አቢ ደምደም ደግሞ ማነው በማለት በግርምት ጠየቋቸው ። እሱማ አሉ ነብያችን ሰለላህ አለይሂ ወሰለም ባነጋ ቁጥር ጧት ላይ በመነሳት ጌታየ ሆይ እኔ ነብሴና ክብሬን ሰጥቸሀለሁ የሚል ሰው ሲሆን የሚሰድቡትን መልሶ አይሰድብም። የበደሉትን አይበድልም የሚመቱትንም መልሶ አይመታም አሏቸው የአቢ ደምደምና የአባታችን አደም አለይሂ ሰላም ልጅ ታሪካቸው ተመሳሳይነት አለው። ወንድሙ ሊገድለው በዛተበት ወቅት እንዲህ በማለት ነበር የመለሰለት ። ልትገድለኝ እጅህን ወደኔ ብትዘረጋ እኔ ልገድልህ እጀን ወደ አንተ የምዘረጋ አይደለሁም እኔ የአለማትን ጌታ አላህን እፈራለሁና አለ ። አቢ ደምደም ታሪኩ አጭር ቢሆንም ከስብዕናው የምናገኘው መልዕክት ግን ግዙፍ ነው በዋናነት ከምፅዋት ወይም ሰደቃ ምንም የሚሰጠው ነገር የለለው ሰው ስምና ክብሩን አሳልፎ በመስጠት ብቻ እሱን ያሙ ሰዎች ወንጀል ዉስጥ እንዳይወድቁ ዋስትናን ሊሰጣቸው እንደሚችልም እንማራለን ። ቢያሙኝም በኔ ምክንያት መጠየቅ የለባቸውም ስጋየ ለነሱ ሀላል ነዉ የሚል ይመስላል አቢ ደምደም። ወዳጆቸ በኔ ምክንያት አንድም ሰዉ መጠየቅ የለበትም ማለት ምንኛ ለሰው ልጅ ማዘንና መቆርቆር ነዉ። የዘመናችን የሰብዓዊ መብት ታጋዮችስ ይህን ያህል ተጉዘው ይሆን? ብቻ የአቢ ደምደም ነገር ይገርማል በምፅዋት ወይም ልግስና ዙሪያ ታዋቂው ኢማም ኢብኑል ቀዩም ሲናገሩ ልግስና አስር ደረጃዎች አሉት ካሉ በኋላ ከነዚህ መካከል የራስን ክብርና ስም መስጠትን በሰባተኛ ደረጃ ላይ ቆጥረዋል ። ወዳጆቼ ሆይ የአቢ ደምደምን ሁኔታ ሳስበው ዉስጡ እንዲህ የሚል መሰለኝ ጌታየ ሆይ ሰዎች ሁሉ ከገንዘብ እና ንብረት የሚለግሱት ነገር አላቸው እኔ ግን የምሰጠውም የምለግሰዉም ነገር የለኝምና ይህንኑ ስጦታየን ተቀበለኝ የሰደበኝና ያማኝን ሰዉ ሁሉ ነፃ ነህ ዕዳ የለብህም በኔ ምክንያት አትቀጣም ብየዋለሁ ። ታዲያ ለዚህም ነው ነብዩ ሰለላህ አለይሂ ወሰለም በአቢ ደምደም ሁኔታ በመደነቅ ይመስላል ማነው ከእናንተ ዉስጥ መሆን የሚችለው በማለት የሚጠይቁት በእርግጥ ነገሩ አላህ ሱበሀነወ ተአላ ላገራለት ሰው ካልሆነ በስተቀር እጅግ ከባድ ነው ። ወዳጆቸ ሆይ አንዳንድ ጊዜ ባላሰብነዉ መልኩ ከግብራችን ጋር የማይዛመዱ ስም ሊሰጠን ይችላል ለማስተካከል ስንወድቅ ስንነሳ ለድናችን ስንሮጥ ለዑማዉ ስንታትር ስንፅፍ ስንናገር ስንከራከር ፈፅሞ የማይመስልና ያልጠበቅነውን ነገር ልንባል እንችላለን ። ያላንዳች ጥቅም የማንሮጥ ተደርጎም ሊወራብን ይችላል እዉነተኛ የአላህን ዉዴታ ፈልገንና ለድኑ አስበን የምንሰራ ከሆነ ምንም እንኳን የሚወጡልንና የሚሰጡን ስሞች ከባድ አሳማሚና አስደንጋጭ ቢሆኑም ፈፅሞ ልንሸበር አይገባም ባይሆን እንደ አቢ ደምደም እንሁን ። የሰደበንን መልሰን አንስደብ የበደለንን አንበድል የመታንን ለመምታት አንጋበዝ ከማሀይማን ጋር ጊዜ አናጥፋ። እነሱ አላወቁም ና ይቅር እንበላቸው ያኔ በአላህ ፍቃድ የሁለቱንም አለም ስኬት እንጎናፀፋለን ። እንደ አቢ ደምደም እንሁን ሰው እንዲህ አለኝ ብለን አንጨነቅ ሰዉ ስላለ አይሙቀን ሰዉ ስላላለም አይብረደን ደረታችን ትግስታችን ፅናታችን ይቅርታችን ሰፊ ይሁን ። የበደሉን ሰዎች ካሉ የመጀመሪያዎቹ ተጎጅዎች እነሱ ራሳቸው ናቸውና እንዘንላቸዉ። ላጠፉብን ይቅር እንበላቸው ከይቅርታ በላይ ጣፋጭ ነገር የለምና ወዳጆቸ ሆይ ከድርጊት በፊት የነገሮችን ትርፍና ኪሳራ ከወዲሁ መገመትና ማመዛዘን ብልህነት ነው ። አዎን የዋህነት ሞኝነት አይደለም ። መታገስና መፍራት የተለያዩ ነገሮች ናቸው በትንሹ በትልቁ ከሰዎች ጋር መጋጨት ከመሀይማን ጋር መጣላትና መልስ መሰጣጠት የጥሩ አማኝ ባህሪ አይደለም ። ምንም ለነገሮች መስጠት የሚቻል ቢሆንም ሰምቶ መቻናልና ንቆ መተዉ ለበለጠ ዉጤት የሚያበቃ ከመሆኑም በላይ የበሳልነት ምልክት ነዉ። https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg

ሰለምቴዋ ሰላማዊት ነኝ የእንዴት ሰለምኩኝ ታሪኬን ለቅምሻ ሹክ ማለትን ወደድኩኝ ። ነገሩ እንዲህ ነው ። ከቤታችን አዲስ ዲሽ እያስጫንን ነበርና የፊልም ጣቢያዎችን ስፈልግ ድንገት የአፍሪካ ቲቪ ቻናልን ተመለከትኩኝ ። በስህተት ነበር የተጫነው ይህ ቻናል ። እኔም በዛን ሰኣት በቲቪው የሚተላለፈውን ፕሮግራም መከታተል ጀመርኩኝ ።በዛን ጊዜ በሙሐመድ ካሚል ኑር የቀረበ ሲሆን ስለ ነቢዩ ሙሐመድ እዝነት ነበር የሚወራው። እርሱም ፦ይህንን ንግግር ነበር በድንገት ያደመጥኩት ከእለታት አንድ ቀን ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ ) ዘንድ አንድ ከገጠር የመጣ ኑሮው ያልሰመረለት (ድኃ) ግለሰብ ሰሃን ሙሉ ወይን ስጦታ ያመጣላቸዋል ነቢዩም (ﷺ ) ስጦታውን ተቀብለው ወይኑን መብላት ጀመሩ.. የመጀመሪያውን ጎርሰው ፈገግ አሉ... ሁለተኛውንም ወይን ጎርሰው ፈገግ አሉ.. ያ ባለ ወይኑ የገጠሩ ሰው በነቢዩ ፈገግታ እጅጉን ተደሰተ.. የነቢዩ ጓዶች (ሰሃቦች) ሁሌም ለነቢዩ (ﷺ) ስጦታ ሲመጣላቸው ስለሚያካፍሏቸው ይህንን (ጣፋጭ) ወይን እንዲያካፍሏቸው በጉጉት ይጠብቃሉ.. የአላህ መልእክተኛ(ﷺ ) ግን ሳያካፍሏቸው እያንዳንዱን የወይን ፍሬ እየበሉ እና ፈገግ እያሉ ሁሉንም በልተው ጨረሱ.. ስጦታ አቅራቢው ሰውም እጅግ በጣም ተደስቶ..ስጦታውንም ስለወደዱለት አመስግኖ ሄደ... አንድ የነቢይ (ﷺ) ጓድ (ሰሃባ) ጠጋ ብሎ ነቢዩን ጠየቃቸው ‹‹የአላህ መልእከተኛ ሆይ..ምን ነው ሳያካፍሉን.? አሏቸው !›› እሳቸውም ﷺ ፈገግ ብለው መለሱ ‹‹ሰወዬው መደሱቱን አይታችኋል አይደል?!..ወይኑን ስቀምሰው በጣም ይመር ነበር.. ኮምጣጣ ነበር ባካፍላችሁ አንዳችሁ ግለሰቡን የሚያስከፋ እና ደስታውን የሚያደፈርስበትን ነገር እንዳታሳዩት ሰጋሁ..!!›› በማለት መለሱ ። ፊዳ'ከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱለሏህ ..!ﷺ ይህን ንግግር ሳበኝ ከዛም እምነቱን ለማወቅ ልቤ ተነሳሳ በዚሁ አጋጣሚ ኢሥላማዊ የቲቪ ቻናሎች እንዲጨመሩ አደረኩኝ ነሲሃ-ቲቪ ቻናልን አስጫንኩኝ መከታተልም ጀመርኩኝ ። ነሲሃ-ቲቪ አብዝሃኛውን ዳዕዋዎች እና ስለ ቁርኣን ነበር እያስተላለፈ ያለው ። እንግዲህ ለእሥልምናዬ የማስተዋል ሰበብ የሆነኝ ይህ ቢሆንም እሥልምናን ስቀበል ከቤት ተባርሬ በሰው ቤት ተቀጥሬ ለዲኔ ዋጋ ስከፍል ነበር ።ያም ሆኑ የሚገርመው እናቴ እህቴ ጎረቤቶችን እሥልምናን እንዲቀበሉ ሰበብ ሆኛለው ።መሉ ታሪኬ በአስሓቡል የሚን ሥር በዩቱብ ቻናላቸው በቅርብ ቀን የማቀርብ ይሆናል ። ሰላማዊት ታሪክ ለቅምሻ የተወሰደ ። እንዴት ወደ ቤተሰቦቿ በድጋሚ ልትመለስ ቻለች? እንዴት ቤተሰቦቿ እሥልምናን ሊቀበሉ ቻሉ ? ሰበቡ ምን ይሆን? ከዚህ አልፏ ወደ እውነት ጎዳና ጎረቤትን ሁሉ እየጠራች በራቸው እያንኳኳች ትገቻለች ። ሙሉ ታሪክ በቅርብ ቀን ............... https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q ቤተሰብ ይሁኑ አሁንም ባለ ታሪክ ለሆኑ ሰለምቴዎች በራችን ክፍት ነው ይላል የአስሓቡል የሚን ጀመዐ ። ሰለምቴዎችን እንጋብዛለን ። እርሶ ሰለምቴ ኖት..!? እንግዲያውስ ታሪኮ ለሌሎች መማሪያ ይሆን ዘንድ ። ለአንዲት ነፍስ የሒዲያ ሰበብ ሊሆን ይችላልና ታሪኮን ያካፍሉን ። አድራሻችን ፦ የሰለምቴዎች ግሩፕ http://t.me/Selmeta ቴሌግራም 00966597257492 http://t.me/Ohanw9 እህት ሐድል 00966503917209 http://t.me/OBintMahmud እህት የትም ወርቅ በዋትስ-አፕ 00966554225870 https://t.me/Quran_is_life_Sari_A እህት ሳራ ቴሌግራም ቻናል፦ http://t.me/AshaBuleyamine የፕሮግራሙ መገኛ ዩቱብ፦ https://m.youtube.com/watch?v=ssov6TY3yzc&feature=youtu.be ሠለምቴ የሆኑ ይምጡ ለመሥለም የሒዳያ ሠበበዎን ያካፋሉን! እኛም ለሌሎች አሥተማሪ በሆነ መልኩ እያዘጋጀን እናቀርባለን። https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg