Posts

ሰለምቴው አብዲሳ.....! እሥልምና መርጦኛል ። ቢስሚላህ አልሃምዱሊላህ አስላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ የአስሓቡል የሚን ቤተሰቦች ። ስሜ አብዲሳ እምሩ ይባላል የምኖረው በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ(አሰበ ተፈሪ) ሲሆን በአሏህ እዝነት ታሪኬን ላካፍላችሁ ወደጃለው አሏህ በራህመቱ በ2010 የኦርቶዶክስ ፆም ውስጥ ነበር የሰለምኩት(ከክህደት አለም የወጣሁት) ነገሩ ወዲህ ነው ስምንተኛ ክፍል እስክደርስ ድረስ የኖርኩት ካፊሮች (ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች) የሚበዙበት ሰፈር ነው ግን ልክ 2008 አካባቢ ስምንተኛ ክፍል ሳለው ሙስሊሞች ሚበዙበት ሰፈር 90% የሚሆኑት የሰፈሩ ነዋሪዎች ሙስሊም የሆኑ ሰፈር ገባን ሁለት አመት እዛ ከኖርን በኃላ ከሰፈሩ ሰው እየተላመድን ስንመጣ እኔም ከሙስሊም ልጆች ጋር ጓደኝነት ጀመርኩ ይሄን ጊዜ ነው እንግዲ የሂዳያ ስጦታዬን ለማግኘት ጉዞ የጀመርኩት። ለጥናት ከሙስሊም ልጆች ጋር በምንገናኝበት ጊዜ ስለእምነት Discuss እናደርግ ነበር ።አንዳንዴም የከፋ ሙግት አደርግ ነበር! ከሙስሊም ጓደኞቼ ሀዲሶችን እሰማ ነበር ብዙ ጊዜ የእየሱስ ክርስቶስ (ነቢ ኢሳ) አሌይሂ ሰላም አልሞተም አልተሰቀለም የምትለዋን ነገር ስሰማ በጣም እናደድ ነበር። አንዳንድ ቀን ለብቻዬን ቁጭ ብዬ ልስለም አልስለም ብዬ ከአእምሮዬ ጋር ግጥሚያ ጀመርኩ ........."አሁን ልስለም ብል ቤተሰቦቼን ትቼ ነው ምሰልመው አይ ይቅርብኝ እነሱን ትቼ ከምሰልም ይቅርብኝ አይ" ብዬ ከአእምሮዬ ጋር ከባድ ጦርነት ገጥም ነበር ግን ከእለታት አንድ ቀን የህይወቴ turning point (ህይወቴ የተለወጠበት) ቀን ላይ ደረስኩ ትዝ ይለኛልእኔ እና ሁለት የሙስሊም ጓደኞቼ ቁጭ ብለን ባለንበት ምላሴ ከአእምሮዬ ጋር ሳይማከር በድንገት ሙስሊም መሆን ፈልጋለው የሚል ቃል ተናገረ! ከዛ እነሱም የሰሙትን ማመን አቅቷቸው እ እ እያሉ በግርምት ያዩኝ ጀመር እኔም በድጋሚ አው ሙስሊም ለመሆን ምን ማድረግ አለብኝ ብዬ ጠየኳቸው እነሱም ምንም ማድረግ አይጠበቅብህም ሸሀዳ ብቻ ማለት ነው ሚያስፈልግህ ከአንገቴ ላይ የሺርክ ገመድን(መስቀል) ፈትቼ ሸሀዳ (መሬት ላይ ያለ ነገር በሙሉ የሷን ያህል መመዘን የማይችለውን ቃል) አልኩኝ በአሏህ እዝነት አልሀምዱሊላህ ወደ ተወለድኩበት እምነት ወደ እስልምና ተመለስኩ ወርቃማ ብዬ መግለፅ ማልችለው ስጦታ ከአሏህ ተበረከተልኝ............. .ኢንሻ አሏህ ክፍል ሁለት ይቀጥላል አብዲሳ ነኝ ሠለምቴው ። ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ የሠለምቴዎችን ታሪክ ለመከታተል ይወዳጁን ዩቱብ https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q ቴሌግራም http://t.me/AshaBuleyamine የፌስ-ቡክ ገጽ https://www.facebook.com/Ashabuleyamine/ አስተያየት ካሎት በድምጽም ሆነ በጹሑፍ መልክ ያስቀምጡ ይደርሰናል 👇 http://t.me//Ashabulyeminbot የሠለምቴዎች እንግዳ መቀበያ http://t.me/Selmeta

Image

የተለመደው የእንዴት ሰለምኩኝ ፕሮግራም ከአዲስ እንግዳ ጋር በአዲስ ታሪክ ቀጥሏል ። የዛሬው የሠንበት ተማሪ የነበረው ሠለምቴ ወንድማችን ታሪክ በቁጥር 26 እንሆ https://www.youtube.com/watch?v=goVH-yHd4o8 እርስዎም ይወዳጁን AS-HABULE YAMLNE TUBE #subscribe https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q #Telegram _Join https://t.me/AshaBuleyamine/4564 የሠለምቴዎች እንግዳ መቀበያ 👇👇 https://t.me/Selmeta

Image

ሰለምቴዋ ሰላማዊት ነኝ የእንዴት ሰለምኩኝ ታሪኬን ለቅምሻ ሹክ ማለትን ወደድኩኝ ። ነገሩ እንዲህ ነው ። ከቤታችን አዲስ ዲሽ እያስጫንን ነበርና የፊልም ጣቢያዎችን ስፈልግ ድንገት የአፍሪካ ቲቪ ቻናልን ተመለከትኩኝ ። በስህተት ነበር የተጫነው ይህ ቻናል ። እኔም በዛን ሰኣት በቲቪው የሚተላለፈውን ፕሮግራም መከታተል ጀመርኩኝ ።በዛን ጊዜ በሙሐመድ ካሚል ኑር የቀረበ ሲሆን ስለ ነቢዩ ሙሐመድ እዝነት ነበር የሚወራው። እርሱም ፦ይህንን ንግግር ነበር በድንገት ያደመጥኩት ከእለታት አንድ ቀን ነቢዩ ሙሐመድ (ﷺ ) ዘንድ አንድ ከገጠር የመጣ ኑሮው ያልሰመረለት (ድኃ) ግለሰብ ሰሃን ሙሉ ወይን ስጦታ ያመጣላቸዋል ነቢዩም (ﷺ ) ስጦታውን ተቀብለው ወይኑን መብላት ጀመሩ.. የመጀመሪያውን ጎርሰው ፈገግ አሉ... ሁለተኛውንም ወይን ጎርሰው ፈገግ አሉ.. ያ ባለ ወይኑ የገጠሩ ሰው በነቢዩ ፈገግታ እጅጉን ተደሰተ.. የነቢዩ ጓዶች (ሰሃቦች) ሁሌም ለነቢዩ (ﷺ) ስጦታ ሲመጣላቸው ስለሚያካፍሏቸው ይህንን (ጣፋጭ) ወይን እንዲያካፍሏቸው በጉጉት ይጠብቃሉ.. የአላህ መልእክተኛ(ﷺ ) ግን ሳያካፍሏቸው እያንዳንዱን የወይን ፍሬ እየበሉ እና ፈገግ እያሉ ሁሉንም በልተው ጨረሱ.. ስጦታ አቅራቢው ሰውም እጅግ በጣም ተደስቶ..ስጦታውንም ስለወደዱለት አመስግኖ ሄደ... አንድ የነቢይ (ﷺ) ጓድ (ሰሃባ) ጠጋ ብሎ ነቢዩን ጠየቃቸው ‹‹የአላህ መልእከተኛ ሆይ..ምን ነው ሳያካፍሉን.? አሏቸው !›› እሳቸውም ﷺ ፈገግ ብለው መለሱ ‹‹ሰወዬው መደሱቱን አይታችኋል አይደል?!..ወይኑን ስቀምሰው በጣም ይመር ነበር.. ኮምጣጣ ነበር ባካፍላችሁ አንዳችሁ ግለሰቡን የሚያስከፋ እና ደስታውን የሚያደፈርስበትን ነገር እንዳታሳዩት ሰጋሁ..!!›› በማለት መለሱ ። ፊዳ'ከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱለሏህ ..!ﷺ ይህን ንግግር ሳበኝ ከዛም እምነቱን ለማወቅ ልቤ ተነሳሳ በዚሁ አጋጣሚ ኢሥላማዊ የቲቪ ቻናሎች እንዲጨመሩ አደረኩኝ ነሲሃ-ቲቪ ቻናልን አስጫንኩኝ መከታተልም ጀመርኩኝ ። ነሲሃ-ቲቪ አብዝሃኛውን ዳዕዋዎች እና ስለ ቁርኣን ነበር እያስተላለፈ ያለው ። እንግዲህ ለእሥልምናዬ የማስተዋል ሰበብ የሆነኝ ይህ ቢሆንም እሥልምናን ስቀበል ከቤት ተባርሬ በሰው ቤት ተቀጥሬ ለዲኔ ዋጋ ስከፍል ነበር ።ያም ሆኑ የሚገርመው እናቴ እህቴ ጎረቤቶችን እሥልምናን እንዲቀበሉ ሰበብ ሆኛለው ።መሉ ታሪኬ በአስሓቡል የሚን ሥር በዩቱብ ቻናላቸው በቅርብ ቀን የማቀርብ ይሆናል ። ሰላማዊት ታሪክ ለቅምሻ የተወሰደ ። እንዴት ወደ ቤተሰቦቿ በድጋሚ ልትመለስ ቻለች? እንዴት ቤተሰቦቿ እሥልምናን ሊቀበሉ ቻሉ ? ሰበቡ ምን ይሆን? ከዚህ አልፏ ወደ እውነት ጎዳና ጎረቤትን ሁሉ እየጠራች በራቸው እያንኳኳች ትገቻለች ። ሙሉ ታሪክ በቅርብ ቀን ............... https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q ቤተሰብ ይሁኑ አሁንም ባለ ታሪክ ለሆኑ ሰለምቴዎች በራችን ክፍት ነው ይላል የአስሓቡል የሚን ጀመዐ ። ሰለምቴዎችን እንጋብዛለን ። እርሶ ሰለምቴ ኖት..!? እንግዲያውስ ታሪኮ ለሌሎች መማሪያ ይሆን ዘንድ ። ለአንዲት ነፍስ የሒዲያ ሰበብ ሊሆን ይችላልና ታሪኮን ያካፍሉን ። አድራሻችን ፦ የሰለምቴዎች ግሩፕ http://t.me/Selmeta ቴሌግራም 00966597257492 http://t.me/Ohanw9 እህት ሐድል 00966503917209 http://t.me/OBintMahmud እህት የትም ወርቅ በዋትስ-አፕ 00966554225870 https://t.me/Quran_is_life_Sari_A እህት ሳራ ቴሌግራም ቻናል፦ http://t.me/AshaBuleyamine የፕሮግራሙ መገኛ ዩቱብ፦ https://m.youtube.com/watch?v=ssov6TY3yzc&feature=youtu.be ሠለምቴ የሆኑ ይምጡ ለመሥለም የሒዳያ ሠበበዎን ያካፋሉን! እኛም ለሌሎች አሥተማሪ በሆነ መልኩ እያዘጋጀን እናቀርባለን። https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg

Image

ነገ የረመዳን ዋዜማ የሻዕባን ማሟያ ነው! በሁሉም የሳውዲ አካባቢዎች ጨረቃ አልታየችም። ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንዳደረሱን በተሚዝ አካባቢ ያለው የጨረቃ መጠባበቂያ ማእከል ውጤት ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን ሆኖም ጨረቃ አልታየችም። በመሆኑም ነገ ሰኞ ሚያዝያ 4/2013 የረመዳን ዋዜማ የሻዕባን የመጨረሻ ቀን ይሆናል። ማክሰኞ ደግሞ ረመዳን 1 ይሆናል። ከሳውዲ ከፍተኛ ፍርድቤት ይፋ መግለጫ በመጠበቅ ላይ ነው። ነሲሓ ቲቪ መላውን ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ እያለ አላህ ተውበትና መልካም ስራን እንዲያገራልን እንለምነዋለን። ረመዳን ሙባረክ! ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉን 👇 https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg

Image

AS-HABULE YAMINE Family Ramadan Mubarak 🌘 كل عم وانتم بالف خير https://youtube.com/channel/UCGL4i2pl7eV7sWA3yvsno_Q

Image

በአንድ ወቅት ነቢዩሏህ ሱለይማን ዐለይሂ ሰላም አንዲት ጉንዳን ከድንጋይ መኃል ያገኛሉ ። ጉንዳኗም አብሯት አንድ ፍሬ ስንዴ አጠገቧ ነበር ። ነቢ ሱለይማንም ዐለይሂ ሰላም " እዚህ ድንጋይ መኃል እየኖርሽም አሏህ ይረዝቅሻልን ?! " ብለው ይጠይቋታል ። እርሷም " አዎን አሏህ ምን ይሳነዋል ?! " ብላ መለሰች ። " ለመሆኑ ይህች አንዷ የስንዴ ፍሬ ለምን ያክል ጊዜ ትበቃሻለች " ሲሉም ይጠይቋታል ። እርሷም " ለአንድ ዓመት ይበቃኛል !! " ስትል መለሰች ነቢዩ ሱለይማንም ዐለይሂ ሰላም " እስቲ እኔ ዘንድ ለአንድ አመት ላቆይሽ " ብለው በመውሰድ አንድ የስንዴ ፍሬ ሰጥተው ያስቀምጧታል ። በአመቱም ጉንዳኗን ለማየት ወዳለችበት ሲሄዱ ግማሹን የስንዴ ፍሬ በልታ ግማሹን አስቀምጣዋለች ። ነቢዩ ሱለይማንም ተደንቀው " ለአንድ ዓመት አንድ የስንዴ ፍሬ ይበቃኛል ብለሽኝ አልነበረምን ?! ታዲያ ግማሹን በልተሽ ግማሹን ለምን ተውሽው ?! " ሲሉ በአግራሞት ይጠይቋታል ። እርሷም " መጀመሪያ ለአንድ አመት አንድ ፍሬ ስንዴ ይበቃኛል ያልኩት እኮ በአሏህ እጅ ላይ ሆኜ ነው !! አሁን ግን በአንንተ እጅ ስለገባሁ ሰው ነክና ልትረሳኝ ትችላለክ ብዬ ግማሹን በልቼ ግማሹን ደግሞ ለምናልባት ብዬ አስቀረሁት !! " ስትል መለሰችለት ። ከጉንዷን ብልህነትን እንማር ። ተስፋችን በአሏህ ላይ ይሁን ።

Image

እስልምናን ለማጥቃት ሲል ግን በእስልምና የተማረከው ጀግና..! ክፍል 1 ዛሬ እስኪ አንድ ጀግና ላስተዋዉቃችሁ እስልምናን ለማጥቃት ሲል ግን በኢስላም የተማረከ ጀግና share አድርጉት በልጅነት እናትና አባቱ ከአገር ይወጣሉ። በዚህ አጋጣሚ በእናቱ እናትና አባት በአያቶቹ እጅ ያድጋል። ክርስትናም አዲሱ ገበያ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን ያስጠምቁታል። በልደታ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በር ላይ አንድ ፕሮቴስታንት ኢየሱስ ጌታ ነው እያለ ሲሰብክ ቴሌ የቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ ገፍትረው በድንጋይ የማርያም ጠላት እየተባለ በድንጋይ ወግረው ሲገሉት ያያል። በመቀጠል ጎፋ ገብርኤል ደጅ ላይ ድግምት የተሰራበት ሰው እንቁራሪት ሲያስታውክ ያያል። ያንን ድርጊት ሲያይ በቀጥታ ከኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ይሰናበታል። በመቀጠል ኢየሱስ ጌታ ነው ወደሚሉት ፕሮቴስታንት ሰሜን መሰረተ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን በመነጋገር ኢየሱስን የግል አዳኙ አድርጎ ተቀበለ። የደህንነት ትምህርት ከተማረ በስድስት ወሩ የውኃ ጥምቀት ወስዶ ተከታታይ ኮርስ ወሰደ። በዚህ ወቅት ላይ መጽሐፍ ቅዱስን ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ በግሉ ማንበብ እና የተለያዩ ማብራሪያዎችን መመልከት ጀመረ። ይህንን የአብነት ትምህርት እየተማረ በተጓዳኝ የአስኳላ ትምህርት ኢለመንተርይ ጨርሶ ሃይስኩል ገባ። ከዚያ ከሃይስኩል ወደ ፕሪፓቶቴርይ ከፕሪፓራቶሪ ወደ አምስት ኪሎ ዩንቨርስቲ ቅርንጫፍ ወደሆነ የህንጻ ምህንድስና 5 ዓመት ካጠናቀቀ በኃላ። ከአገር ይወጣል። ካገር ከወጣ በኃላ ስቶክሆል ዩንቨርስቲ በማቴሪያል ኢንጅነሪንግ እየተማረ እያለ በግቢ ውስጥ በሚደረገው የፍልስፍና የስነ ልቦና እና የስነ አመክንዮ ውይይት ላይ መሳተፍ ጀመረ። አንድ ጓደኛው ፓል ቶክ የሚባል የውይይት መድረክ አለ እዛ ገብተህ ብታተረማምሳቸው ጥሩ ነበር አለው። ወደ ሳይበሩ ዓለም ሲመጣ አጋጣሚ ክርስትና እና እስልምና የሚፋጠጡበት መድረክ ነበር። ከኢትዮጵያ ኡስታዝ አቡሃይደር ከፈረንሳይ በረከት የሚባሉ ጠንካራ ተወያዮች ሁለት የተለያየ ግሩፕ መስርተው ይወያዩ ነበር። በዚህ ወቅት ነው የክርስትናውን መድረክ የተቀላቀለው። ይቀጥላል...... እርሶ ሰለምቴ ኖት..!? እንግዲያውስ ታሪኮ ለሌሎች መማሪያ ይሆን ዘንድ ። ለአንዲት ነፍስ የሒዲያ ሰበብ ሊሆን ይችላልና ታሪኮን ያካፍሉን ። አድራሻችን ፦ http://t.me/Selmeta ቴሌግራም 00966597257492 http://t.me/Ohanw9 00966503917209 http://t.me/OBintMahmud በዋትስ-አፕ 00966554225870 https://t.me/Quran_is_life_Sari_A የፕሮግራሙ መገኛ ዩቱብ https://youtu.be/aU23u6NuZTo የአስሓቡል የሚን ማህደር፦ https://t.me/joinchat/AAAAAEV2Kb4hUy-9DkHbtg ሠለምቴ የሆኑ ይምጡ ለመሥለም የሒዳያ ሠበበዎን ያካፋሉን! እኛም ለሌሎች አሥተማሪ በሆነ መልኩ እያዘጋጀን እናቀርባለን።

Image